Application Form የኮሌጁ ሰራተኞች በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ውጤታማ ተሳትፎ ማድረጋቸው ተገለፀ

የኮሌጁ ሰራተኞች በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ውጤታማ ተሳትፎ ማድረጋቸው ተገለፀ

05th August, 2025

የኮልፌ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ አመራር እና ሰራተኞች በሐገር አቀፍ ደረጃ በመትከል ማንሰራራት በሚል መሪ ቃል እየተከናወነ በሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ከተያዘው እቅድ አኳያ ውጤታማ ተሳትፎ ማድረጋቸውን የኮሌጁ ዲን ገልፀዋል፡፡

የኮሌጁ ዲን ዶክተር ቢኒያም አወቀ እንደገለጹት በአንድ ጀንበር 700 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሃ ግብር ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የኮሌጁ አመራር እና ሰራተኞች ከማለዳው 12 ፡ 00 ሰዓት ጀምሮ በትንሹ አስር ችግኞችን በነፍስ ወከፍ የመትከል እቅድን ለማሳካት ሁሉንም የኮሌጁ ሰራተኞች ባሳተፈ ሁኔታ ዘነብ ወርቅ አካባቢ በተዘጋጀ የችግኝ መትከያ ቦታ ላይ  ተሰማርተው በርከት ያሉ ሃገር በቀል ቸግኞችን መተከላቸውን አስታውቀዋል፡፡

.

Copyright © All rights reserved.

Created with