የኮልፌ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የንብረት አስተዳደር ቡድን የ 2017 ዓ.ም አመታዊ የንብረት ቆጠራ እየተካሄደ መሆኑን አሳዉቋል፡፡
የንብረት አስተዳደር ቡድን መሪ ወ/ሮ ትዕግስት ተስፋየ እንደገለፁት አላቂ እና ቋሚ ንብረቶችን የመቁጠር እና መለያ የመለጠፍ ስራ በቆጠራ ኮሚቴዎች አማካኝነት እየተከናወነ እንደሚገኝ በመግለጽ የኮሌጁ ሰራተኞች አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉላቸው ጠይቀዋል፡፡